ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ የሰለጠናቸውን 511 ተማሪዎችን አስመርቋል።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ የሰለጠናቸውን 511 ተማሪዎችን አስመርቋል። 

ከተመራቂዎቹ 363ቱ ከጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና ከሕግ ት/ቤት በመጀመሪያ ዲግሪ በመደበኛ፣ በተከታታይ እና በክረምት ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።

ቀሪዎቹ 148 ተማሪዎች በሁለተኛ ዲግሪ በመደበኛ ፕሮግራም ስልጠናቸውን እንደተከታተሉ የዩኒቨርሲቲው የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር ዳንኤል ሰይፉ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል። 

ከጠቅላላ ተመራቂዎቹ 74ቱ (22 በ2ኛ ዲግሪ) ሴት ተማሪዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። 

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ 2 ሺህ 844 ተማሪዎችን ባለፈው ሰኔ በመጀመሪያ እና 2ኛ ዲግሪ ማስመረቁ ይታወሳል።