በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርትን በሚመለከት የሥርዓተ ትምህርት ግምገማ ተካሄደ።
Posted by admin on Wednesday, 30 April 2025

ሚያዚያ 11/2017 ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
የዩኒቨርሲቲው የልህቀት ማዕከል ከሆኑት አንዱ ጤና ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በዘርፋ በሁለተኛ ዲግሪ ደረጃ በሚሰጡ ትምህርት ፕሮግራሞች ዙሪያ የኮሌጁ መምህራን እና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የሥርዓተ ትምህርት ግምገማና ፍተሻ ተካሂዳል።
መንግስት በአሁኑ ሰዓት ለትምህርት ጥራት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ በመሆኑ ይህንኑ በመደገፍ እንዴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም በጥራቱ ዙሪያ የተጠናከረ ሥራ ለመሥራት እና በጤና ኢንስቲትዩቱ በባዮ ሜዲካል ላብራቶሪና በጄነራል ፓብሊክ ሄልዝ የሦስተኛ ዲግሪ ትምህርት ለመጀመር ታስቦ የተዘጋጀ መድረክ ስለመሆኑ በም/ፕሬዝዳንት ማዕረግ የጤና ኢንስቲትዩት ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ሳፋይ ኤለማ አስረድቷል።
የኢንስቲትዩቱ መ/ር በሆኑት በመምህር አንተነህ አማካኝነት በአሁኑ ሰዓት አጠቃላይ በጤና ኮሌጁ በሁለተኛ ዲግሪ ደረጃ በሚሰጡ ፕሮግራሞች ዙሪያ ተማሪዎችን ለማብቃት እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች፣የመማር ማስተማር ሥነ ዘዴ፣የተማሪዎች የውጤት ግምገማ ህደት በጽንሰ ሀሳብና በተግባር ደረጃ ምን ይመስላል በሚሉትና በሌሎች ነጥቦች ዙሪያ ለውይይት የሚሆን መነሻ ጽሑፍ ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች የተጋበዙ ምሁራን በበይነ መረብ የነበራቸውን ልምድ አካፍሏል።