በቡሌ ሆራ  ዩኒቨርሲቲ የዩኒቨርሲቲው የአሥር ዓመት የሥራ  ዕቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ

25/12/2014
የቡሌ ሆራ  ዩኒቨርሲቲ  ፕሬዚዳንት ዶ/ር ታምሩ አኖሌ ከዩኒቨርሲቲው የካውንስል አባላት ጋር በዩኒቨርሲቲው የአሥር ዓመት የሥራ  ዕቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡ 
በውይይቱ የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዚዳንቶችን  ጨምሮ የካውንስል አባላቶች ተገኝተዋል፡፡ ከመማር ማስተማር፣ ከምርምር ፣ ከማህበረሰብ አገልግሎት ፣ ከኢንዱስትሪ ትሥሥር  እና ከአጠቃላይ ተቋማዊ የሥራ ትግበራ አንጻር ከ2010 እሰከ 2014 ዓ.ም ድረስ የዩኒቨርሲቲው የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በውይይቱ የቀረበ ሲሆን ከ2015 እሰከ 2024ዓ.ም የዩኒቨርሲቲውን የልህቀት ደረጃ ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀው የተቋሙ ዕቅድም ለካውንስል አበላቱ ቀርቧል፡፡ 

የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ቦርድ በሆስፒታሉ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ውይይት አደረገ

ነሐሴ 22/2014 ዓ.ም
የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ቦርድ በሆስፒታሉ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ውይይት አደረገ። በውይይቱ የሆስፒታሉ ቦርድ አደረጃጀት፣የሆስፒታሉ ቦርድ አመራር ሀላፊነት፣ ክትትል እና ምዘና እንዲሁም አጠቃላይ የስራ ሂደት በስፋት ተብራርቷል ።
የሆስፒታሉን አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ከማሻሻል አንፃር የሆስፒታሉ ቦርድ ሊኖረው ስለሚገባው ሀላፊነትም ሰፊ ውይይት ተካሂዷል ።
የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ቦርድ ሰብሳቢና የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ዳይሬክተር ረ/ፕ ገመዳ ኦዶ የሆስፒታሉ የቦርድ አመራር ፤ከቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ጋር በተቀናጀ እና በተናበበ መልኩ በመስራት የሆስፒታሉን አገልግሎት አሰጣጥ ወደሚፈለገው ደረጃ ማድረስ የጋራ ሀላፊነት መሆኑን በመጠቆም የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ቦርድ አመራር ተገቢውን የድጋፍ እና ክትትል ስራ ማከናወን እንዳለበት ገልፀዋል።

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢኒስቲቲዩት እጩ ምሩቃን ሲሰሩ የቆዩትን ምርምር አቀረቡ

ነሐሴ 11/2014 ዓ.ም
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢኒስቲቲዩት እጩ ምሩቃን ከኢኒስቲቲዩቱ ጋር በመተባበር በማህበረሰብ ጤና ዙሪያ ለሁለት ተከታታይ ወራት ሲሰሩት የቆዩትን ምርምር አቀረቡ።
የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር ገመዳ ኦዶን ጨምሮ የጤና ኢኒስቲቲዩቱ መምህራንና የኢኒስቲቲዩቱ  እጩ ተመራቂ ተማሪዎች ተገኝተዋል። የማህበረሰብን የጤና ችግር ለመፍታት የተደረገዉ Team Training Program(TTP)በተለያዩ አራት ወረዳዎች ሲሆን ዱግደ ዳዋ፣ቡሌ ሆራ፣ ያቤሎ እና ጓንጓ ጥናቱ የተደረገባቸው ወረዳዎች ናቸው።

ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በ2015 በጀት ዓመት የተፈቀደለትን የካፒታል እንዲሁም የመደበኛ በጀት ላይ የፋይናንስ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ውይይት አደረገ

ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በ2015 በጀት ዓመት የተፈቀደለትን የካፒታል እንዲሁም የመደበኛ በጀት ላይ የፋይናንስ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ውይይት አደረገ።
በዉይይቱ ላይ ዳይሬክተሩን ጨምሮ የኮሌጅ፣የመማሪያ ሆስፒታል እንዲሁም የመዓከል የሂሳብ ሰራተኞች   ተገኝተዋል ።
 የዉይይቱም አላማ በ2015 በጀት ዓመት ከኦዲት ግኝት የጠራ እና ግልፀኝነት የተሞላበት አሰራር እንደሚተገበር እንዲሁም ጠንካራ የፋይናንስ ፍሰት እንዴት ማስቻል እንደሚቻል ላይ ያተኮረ ነዉ።

Pages