ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ 'YeQaQe' ከተባለ ሀገር በቀል ግብረሰናይ ድርጅት ጋር የሥራ ማስጀመሪያ ውይይት አካሄደ።

ካቲት 19/2018 ዓ.ም :ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ

ዩኒቨርሲቲዉ 'YeQaQe' ከተባለ እና "New Years to Empower Women and Youth for resilient Citizen" በሚል ሀሳብ በተለየ መልኩ በኢኮኖሚዉ ዘርፍ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከሚሠራ ሀገር በቀል ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር ለመስራት ከዩኒቨርሲቲዉ የሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላትና የድርጅቱ መስራች ወ/ሮ ሙላቱዋ እንዲሁም ከጀርመን ሀገር በድርጅቱ ጋባዥነት ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ከመጡት ፕሮፌሰር አደራጀዉ ዋካ በተገኙበት አጠቃላይ ዉይይት ተደርጎ ቀጣይ በጋራ በሚሠሩ ሥራዎች ዙሪያ አቅጣጨ ተቀምጧል፡፡

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የስራ አመራር ቦርድ የተቋሙን የስድስት ወራት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርትና የ2018 በጀት ዓመት የውስጥ ገቢ እቅድ ግምገማ አካሄደ።

የካቲት 26/2018 ዓ.ም ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ

ሪፖርቱን ያቀረቡት የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ አቶ መሰለ አለማየሁ ሲሆኑ፣ ቁልፍ የውጤት አመላካቾችን አፈፃፀም በየሥራ ዘርፋቸዉ አንፃር በማደራጀት በመማር ማስተማር ፣በምርምር፣ በማህብረሰብ አገልግሎት፣ በአስተዳደር ዘርፍ እና በተቋሙ የልህቀት መስኮች የተከናወኑ ተግባራትን መሠረት በማድረግ ነዉ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ለ15ኛ ጊዜ 1266 ተማሪዎችን በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል።

መጋቢት 13/2018

ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ ኮሌጆች ሲያሰለጥናቸው የቆየውን ተማሪዎች የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የዞንና ከተማ መስተዳድር አመራሮች ፣የዩኒቨርሲቲው ሴኔት አባላት ፣አባ ገዳዎች፣የሐይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም የተማሪ ወላጆች በተገኙበት በመጀመሪያ ድግሪ 992 ተማሪዎች በሁለተኛ ዲግሪ 269 በሦስተኛ ድግሪ ( Ph.D) 5 ተማሪዎችን በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስመርቋል።

በምረቃ በዓሉ ላይ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት በማስተላለፍ ንግግራቸውን የጀመሩት የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ተመስገን ደበሎ ትምህርት የአመለካከት፣የእውቀት እና የክህሎት በመለወጥ ለሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግና የሚያዘጋጅ መሣሪያ መሆኑን እና በዚሁ መልኩ የተለወጠ ዜጋ ለቤተሰቡም ሆነ ለሀገር ለውጥ ይተጋል ሲሉ ገልፀዋል።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን አስመረቀ

መጋቢት 13/2018 ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ

ዩኒቨርሲቲው ከ15ኛ ዙር ተማሪዎች ምርቃት ጎን ለጎን የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት የተቀላጠፈ እንዲሆን በማድረግና የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ በኩል ትልቅ ሚና የሚጫወቱ እንዲሁም የማህብረሰቡን ተጠቃሚነት እንዲያረጋግጡ ታስበው የተገነቡ ሦስት ትላልቅ ፕሮጀክቶችን በትምህርት ሚኒስቴር የምርምር እና ማህብረሰብ አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚና የዕለቱ የክብር እንግዳ ክቡር ዶ/ር ሠራዊት ሃንዲሶ እና ለሎችም የትምህርት ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎችና የምዕራብ ጉጂ ዞን አስተዳደር አካላት በተገኙበት አስመርቋል።

Pages