በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ /College of Natural and Computational Science /አስተባባርነት በቅርቡ በሀገራችን እየተከሰተ ስለአለው የመሬት መንቀጥቀጥን አስመልክቶ ሴሚናር ተካሄደ፡፡
Posted by admin on Friday, 17 January 2025ጥር 07/2017 ዓ.ም
በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች የመሬት መንቀጥቀጥ እየተከሰተ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ለዩኒቨርሲቲውና ለአካባቢው ማህብረሰብ ግንዛቤ ለማስጨበጥ በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ”College of Natural and Computational Science ``አስተባባርነት የኮሌጁ መምህራን፤የትምህርት ክፍል ኃላፊዎችና ሠራተኞች በተገኙበት ሴሚናር ተካሂዷል፡፡
በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ክንፈ ወ/ጊዮርግስ ሲሆኑ በአሁኑ ሰዓት በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች የመሬት መንቀጥቀጥን ተከትሎ የሚፈጠረውን እሳተ ጎመራን አስመልክው ከሙሁራን እይታ አንፃር ሙያዊ ትንታኔ ለማህብረሰቡ ለመሰጠት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ማስታወቂያ
Posted by admin on Friday, 17 January 2025ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ጥር 02/2017 ዓ.ም(BHU)
የመውጫ ፈተና ለምትጠባበቁ መምህራንና እጩ ተመራቂዎች በሙሉ::
በክረምት መርሓ ግብር በመምህርነት ሙያ ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ድግሪ የትምህርት እርከን ማሻሻያ ስልጠና ስትከታተሉ የቆያችሁና፤እንዲሁም በቅዳሜ እና እሁድ የትምህርት መርሓ ግብር ስትከታተሉ ቆይታችሁ የመውጫ ፈተናውን ያልወሰዳችሁ ሠልጣኞች፤የመውጫ ፈተና የሚሠጠው ከየካቲት 10-12/2017 ዓ.ም ስለሆነ ፈተናው የሚመለከታችሁ አካላት በሙሉ ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ አጥብቀን እናሳውቃለን፡፡
የአካዳሚክ ፕሮግራም ዳይሬክቶሬት
ኢንጅነሪንግ እና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ለላብራቶሪ ባለሙያዎች እና ለሁለተኛ ድግሪ ተማሪዎች በ‹‹ MATLAB››ሶፍት ዌር አጠቃቀም ዙሪያ ሥልጠና ተሰጠ፡፡
Posted by admin on Friday, 17 January 2025ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 28/2017 ዓ.ም (BHU)
የዩኒቨርሲቲዉ ኢንጅነሪንግ እና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ በስሩ ያሉትን የመምህራንና የባለሙያዎችን አቅም በተለያዩ አቅም ግንባታ ሥልጠናዎች ለማጎልበት የተለያዩ ስልቶችን ቀይሶ እየሰራ ይገኛል፡፡
በሥልጠናዉ ዕለት ተገኝቶ መልዕክት ያስተላለፉት የኢንጅነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ዲን መ/ር ቦሩ ቤደያ በኢንጅነሪንጉ ዘርፍ የሚከናወኑ ተግባራት ተያያዥነት ያላቸዉ በመሆኑ ለመምህራን እየተሰጠ ካለዉ የአቅም ግንባታ ሥልጠና በተጨማሪ ለላብራቶሪ ባለሙያዎች እና ለሁለተኛ ድግሪ ተማሪዎች መስጠቱ አስፈላጊ ሆኖ ስለታመነበት በ‹‹ MATLAB››ሶፍት ዌር አጠቃቀም ዙሪያ ሥልጠና መዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡