በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የሰንደቅ ዓላማ ቀን ተከበረ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ(BHU) ጥቅምት 04/2017 ዓ.ም

ለ17ኛ ጊዜ የሚከበረዉን ብሄራዊ የሰንደቅዓላማ ቀን ምክንያት በማድረግ በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የዩኒቨርሲቲዉ ሠራተኞች፤የተለያዩ የፀጥታ አካላት እና ለአቅም ግንባታ ሥልጠና ወደ ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ሥልጠና ማዕከል የገቡ የብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ጭምር በተገኙበት ሰንደቅዓላማዉ ብሔራዊ ክብርን በጠበቀ መልኩ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ፤መዝሙር ተጅቦ እንዲሠቀል የተደረገ ሲሆን በሰንደቅዓላማው ቀን ላይ የተሳተፉ አካላት ቃለ መሃላ በመግባት ወይም በመፈጸም ሥነሥረዓቱ ተጠናቋል ፡፡