በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ለ2016 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና እንዲፈተኑ የተመደቡ ተማሪዎች ወደ መፈተኛ መዕከሉ እየገቡ ይገኛሉ።

ሀምሌ 06/2016 ዓ/ም

በዩኒቨርሲቲዉ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና እንዲፈተኑ የተመደቡ ተማሪዎች ከዛሬ ሀምሌ 06/2016 ዓ/ም ከጠዋቱ 5;30 ጀምሮ ከዙሪያዉ ከሚገኙ ዞኖችና ወረዳዎች ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ቅጥር ግቢ እየገቡ ሲሆን፣ በሁለተኛ ዙር ለፈተናዉ የሚቀመጡ ተማሪዎች ብዛት ወንድ 4624 ሴት 2200 በጥቅሉ 6824 ናቸዉ።  ለተማሪዎቹ በተደረገዉ የአቀባበል ስረዓት ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዝዳንቶችና የስራ አመራሮች ሲሆኑ አቀባበሉን በምርቃት የከፈቱት የአካባቢዉ አባገዳዎችና የሀገር ሽማግሌዎች ናቸዉ።

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የችግኝ ተከላና የምስጋና ፕሮግራም ተካሄደ።

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የ2016 የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ብሄራዊ ፈተና የተፈተኑ ተማሪዎች ፈተናዉን እንዳጠናቀቁ ሀገር አቀፍ የአረጉጓዴ አሻራ ፕሮግራምን ተግባራዊ በማድረግ ሂደት ዉስጥ የረሳቸዉን ድርሻ ለመወጣት በዩኒቨርሲቲዉ ግቢ ዉስጥ የተለያዩ ዛፎችን ተከሉ።  በሀገር አቀፍ በተቀመጠዉ አቅጣጫ መሰረት የመጀመሪያ ዙር ተፈታኝ የሆኑት የማሃበረዊ ሳይንስ ተማሪዎች በችግኝ ተከላዉ ላይ የተሳተፉ ሲሆን በተመሳሳስይ መልኩ በሚቀጠለዉ ሳምንት ለፈተናዉ የሚቀመጡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችም የአረንጓዴ አሻራዉን የማስቀጠልና የመተግበር ፕሮግራም እንደሚያካሂዱ ከወጣዉ ፕሮግራም ለመረዳት ተችሏል።

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በ2016ዓ/ም የ 12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና (Entrance Exam)ለሚወስዱ ተማሪዎች ፈተና እየሰጠ ይገኛል።

ሃምሌ 2016 ዓ/ም

በሀገር አቀፍ ደረጃ በወጣዉ መረሃ ግብር መሰረት ከሃምሌ 3/2016 ዓ/ም ጀምሮ ለሚሰጠዉ ፈተና ዩኒቨርሲቲዉ ሃምሌ 2/2016 ዓ/ም ለሁሉም ተማሪዎች ስለፈተናዉ አሰጣጥና የፈተና ዲሲፕሊን አስመልክቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ ኦረንቴሽን የሰጠ ሲሆን፣ በተመሳሳይ መልኩ ፈተናዉን ለሚሰጡ መምህራንም አጠር ያለ ገለጻ ተሰቶአቸዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ በተቀመጠዉ አቅጣጫ መሰረት ፈተናዉ ከጠዋቱ 3;00 እስከ 5;00 ሰዓት ሊሰጥ የተዘጋጀዉን የእንግሊዘኛ ቋንቋ የተሰጠ ሲሆን በዚሁ ዕለት ከሰዓት በኋላ ከ9;00 እስከ 12;00 ሰዓት የሚሰጠዉን የሂሳብ ትምህርት ተማሪዎች አየወሰዱት ይገኛሉ።

 

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ማጠቃለያ ፈተና (Entrance Exam)የሚወስዱ ተማሪዎችን መቀበል ጀመረ

ዩኒቨርሲቲዉ በ2016 የትምህርት ዘመን የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ማጠቃለያ ፈተና(Entrance Exam)የሚወስዱትን ተማሪዎች በዙሪያዉ ካሉት የተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች ተቀብሎ ለፈተናዉ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ እያስተናገደ ይገኛል።

Pages