የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለዩኒቨረሲቲው በተለያየ ክፍል ባለሙያዎች እና የሰዉ ሀብት ልማት አስተዳደር ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ።

የስልጠናው ትኩረት ከኦዲት ግኝት የፀዳ ተቋም ለመፍጥር በሚያስችሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሲሆን፤ በገንዘብ ሚኒስቴር የኦዲት ኢንስፔክሽን ባለሙያ በአቶ መኮንን መኩሪያ ስልጠናው ተሰቷል።
የበጀት ክትትል፣ የተከፋይ ሂሳብ፣ የግዥ፣ የንብረት አያያዝና አጠባበቅ ስርዓት እንዲሁም ሌሎች ተመሳሳይ የፋይናንስ አጠቃቀም እና አተገባበር የሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች በስልጠናው ዉስጥ ተካተዋል።
የገንዘብ ሚኒስቴርን ደንብ እና መመሪያ ህጉን በጠበቀ መልኩ የፋይናንስ ስርዓቱን ለማክበርና ለማስከበር በሚያስችሉ ፅንሰ ሀሳቦች ላይም ሰፊ ማብራሪያ ተሰቶባቸዋል።

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርሲቲው የፋይናንስ አስተዳደር ሠራተኞች እና ባለሙያዎች በፋይናንስ አስተዳደር ዙሪያ ስልጠና ሰጠ

በስልጠናው ላይ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የፋይናንስ አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ቦሩ ህርባዬን ጨምሮ በረካታ ቁጥር ያላቸው የፋይናንስ ባለሙያዎች ተሳተፈዋል::
በስልጠናው በፋይናንስ አስተዳደር፣ በበጀት ምንነት፣ በክፍያ ሁኔታዎች፣ በጥሬ ገንዘብ አጠቃቀም፣ የበጀት መርህ እቅድን ከበጀት ጋር ማስተሳሰር በሚሉ እና በሌሎች ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ስልጠናው ተሰጠቷል::
በስልጠናው የፋይናንስ አስተዳደርን ለማዳበር እና ውጤታማ የበጀት አጠቃቀምን ለማሳደግ ከፍተኛ ጠቄሜታ እንዳለው የዩኒቨርሲቲው የፋይናንስ አስተዳደር ዳይሬክተሩ በስልጠናው ላይ ገልፀዋል::
በተቋሙ ዉስጥ ለሚከናወኑ የለውጥ ስራዎችና አጠቃላይ የገንዘብ ነክ ጉዳዮች የበጀት አጠቃቀምና ምንነትን ማወቅ አስፈላጊ ስለመሆኑም አንስተዋል::

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የኤሌክትሮኒክስ ባንኪንግ አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና ሰጠ፡፡

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የኤሌክትሮኒክስ ባንኪንግ አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና ሰጠ፡፡
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቡሌ ሆራ ቅርንጣፍ ጋር በመተባበር ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፋይናንስ አስተዳደር ባለሙያዎች በኤሌክትሮኒክስ ባንኪንግ ጋር በተያያዘ ስልጠና ሰጠ፡፡
በስልጠናዉ ላይ ዶ/ር ታምሩ አኖሌ (የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ) ፣ዶ/ር ሮባ ደንቢ (የአስተዳደርና ተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ) እና ዶ/ር ጉሚ ቦሩ (የምርምርና የማህበረሰብ  አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት) ተገኝተዋል፡፡
የኤፌዲሪ ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ባወጣው አዋጅ መሰረት የፌዴራል ፋይናንስ ተቋማት ማንኛውንም ክፍያ በዲጅታል ኤሌክትሮኒክሲ የክፍያዎች መረብ መፈፀም እንዳለበት ይደነግጋል:: 

International Virtual Conference On Transforming Agricultural Advisory Services to Mitigate the Effects of the Pandemic for Farmers Welfare.

Vellore Institute of Technology in collaboration with Bule Hora University and other 2 Universities are organizing an International conference on  “Transforming Agricultural Advisory Services to Mitigate the Effects of the Pandemic for Farmers Welfare”.

Pages