Statistical Package for the Social Sciences (SPSS) and AMOS ›› በሚል ርዕስ ለመምህራን የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተሰጠ፡፡
Posted by admin on Friday, 17 January 2025ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም (BHU)
ሥልጠናዉ የተዘጋጀዉ በብዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ አስተባባሪነት ሲሆን ከተለያዩ የኮሌጁ ትምህርት ክፍሎች የተወጣጡ መምህራንና ሁለተኛ ድግሪያቸውን በተቋሙ እየተከታተሉ ያሉ ተማሪዎች ተሳታፊ ስለመሆናቸዉ ተገልጾዋል፡፡
በቦታው ላይ በመገኘት ስልጠናውን አስመልክተው መልዕክት ያስተላለፉት የብዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ዲን መ/ር ማንዶ ገናሌ ሲሆኑ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትኩረት ተሰጥቶኣቸው እየተከናወኑ ካሉት ተግባራት አንዱ በዋናነት የጥናትና ምርምር ሥራዎች መሆናቸውን በመጥቀስ እነዚህን የምርምር ሥራዎች በተሻሻሉ ሶፍትዌሮች በመደገፍ ጥራት ያላቸዉን የጥናትና ምርምር ሥራዎችን መምህራን እንዲሰሩ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ የአቅም ግንባታ ሥልጠና መሆኑን በንግግራቸው አመላክቷል፡፡
Research Methodology in Social Science: Quantitative and Qualitative research ``በሚል ርዕስ ስልጠና ተሰጠ፡፡
Posted by admin on Friday, 17 January 2025Basic Training on Technology Transfer through Power World Simulator and ETAP soft wares for enhancing the Capacity of Lab assistant and Post Graduate Students``በሚል ርዕስ ሥልጠና ተሰጠ
Posted by admin on Friday, 17 January 2025ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ ታህሳስ 18/2017 ዓ.ም (BHU)
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ‹‹Basic Training on Technology Transfer through Power World Simulator and ETAP soft wares for enhancing the Capacity of Lab assistant and Post Graduate Students``በሚል ርዕስ ሥልጠና ተሰጠ፡፡
ሥልጠናዉ የተዘጋጀዉ በኢንጅነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ስር ከሚገኙት የትምህርት ክፍሎች አንዱ በሆነው በኤሌክትሪካልና ኮምፒዩተር ኢንጅነሪንግ የትምህርት ክፍል አስተባባሪነት ሲሆን በትምህርት ክፍሉ ሥር ያሉትን መምህራን አቅማቸውን በተለያዩ ዘርፎች ለማሳደግና ለማብቃት ታስቦ የተዘጋጀ ሥልጠና መሆኑ በስልጠናው ወቅት ተገልጿል፡፡