በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የፀረ-ጾታ ጥቃት፤የፀረ-ኤድስ እና የአካል ጉዳተኞች ቀን ተከበረ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ ታህሳስ 12/2017 ዓ.ም (BHU)
በዚህ አመት የፀረ-ፆታ ጥቃት በአለም አቀፍ ደረጃ ለ33ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ19ኛ ጊዜ ‹‹የሴቷ ጥቅት የእኔም ነዉ ዝም አልልም! ›› በሚል መሪ ቃል፤ በሌላ በኩል የፀረ-ኤድስ ቀን በአለም አቀፍ ደረጃ ለ37ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ36ኛ ጊዜ ‹‹ሰብዓዊ መብት ያከበረ ኤች አይ ቭ አገልግሎት ለሁሉም!›› እንዱሁም የአካል ጉዳተኞች ቀን በአለም አቀፍ ደረጃ ለ33ኛ ጊዜ በሀገራችን ለ32ኛ ጊዜ ‹‹የአካል ጉዳተኞችን የመሪነት ሚና በማጉላት አካታችና ዘላቂ ልማትን እናረጋግጥ!››በሚል መሪ ቃል የዩኒቨርሲቲዉ የሥራ ኃላፊዎች ፤ሰራተኞችና ተማሪዎች በተገኙበት በተለያዩ መርሃ ግብሮች ታጅቦ በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል፡፡

ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ መጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች የሕይወት ክህሎት ሥልጠና ተሰጠ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 08/2017
ሥልጠናዉ የተዘጋጀው በዩኒቨርሲቲዉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈፃሚ አስተባባርነት ሲሆን ሥልጠናው በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በዩኒቨርሲቲዉ ካሉት የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች በተወጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎች ተሰጥቷል፡፡
በሥልጠናዉ ላይ ተገኝተዉ ተገቢውን መልዕክት ያስተላለፉት የዩኒቨርሲቲዉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሪት ተስፋነሽ ኢዴኤ ሲሆኑ የሥልጠናዉ ዓለማ ወደ ዩኒቨርሲቲዉ እየገቡ ያሉ ተማሪዎች በዕዉቀትና በክህሎት ላይ የተመሠረቱ ዉሳኔዎችን የመወሰን ብቃት በማዳበር በህይወታቸዉ ዉስጥ የሚገጥማቸዉን ፈተናዎች ወደ መልካም አጋጣሚዎች በመቀየር ለዉጤት እንዲበቁ ታስቦ የተዘጋጀ ሥልጠና ስለመሆኑ አስረድቷል፡፡

በ2017 የትምህርት ዘመን ለአቅም መሻሻያ (Remedial) ትምህርት ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ ተማሪዎች በመግባት ላይ ይገኛሉ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታኅሣሥ 7 ቀን 2017 ዓ.ም (BHU)
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በ2017 የትምህርት ዘመን ለአቅም መሻሻያ (Remedial) ትምህርት የተመደቡ ተማሪዎችን ታህሳስ 7 እና 8 /2017 ዓ.ም ጀምሮ ምዝገባ ለማከናወን በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ጥሪ ማስተላለፉ ይታወሳል፡፡

የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስቲር ዴኤታና የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ ሰቢሳቢ የሆኑት ዶ/ር ኬይረዲን ተዘራን ጨምሮ የቦርድ አባላት በዩኒቨርሲቲው እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችን አስመልክተው የመስክ ምልከታ አደረጉ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታኅሣሥ 5 ቀን 2017 ዓ.ም (BHU)
ቦርዱ ያደረገዉ የመስክ ምልከታ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲዉ ከሦስት ወራት በፊት ያለበትን የሥራ አፈፃፀም ደረጃ ከገመገመ በኃላ በቀጣይ ሦስት ወራት ዉስጥ መስተካከል አለባቸዉ ብሎ አቅጣጫ ባስቀመጠው መሠረት የተከናወኑ ሥራዎችን ታሳቢ ያደረገ የመስክ ምልከታ እንደሆነ በምልከታው ወቅት ተገልጾዋል፡፡

Pages