events&news

events&news

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ዘርፍ የ3ኛ ሩብ እና የ9 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ

የዘርፉ ያለፉት ዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት እያንዳንዱ የሥራ ክፍል ኃላፊ ሪፖርቱን በማቅረብ የጋራ ግምገማ ተካሂዶባቸዋል። የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማው ትምህርት ሚኒስቴር ያወረደውን  ቁልፍ ተግባራት መነሻ በማድረግ በመማር ማስተማር፣በምርምር እና በማህብረሰብ አገልግሎት በኩል የተከናወኑ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ የሪፖርት ግምገማው ተካሂዷል። ከመማር ማስተማር አኳያ ተመራቂ ተማሪዎች በየ ኮሌጁ የመውጫ ፈተና የማለፍ ምጣኔ፣የማቋረጥና የመመረቅ ምጣኔዎች ከተቀመጠው ስታንዳርድ አንፃር ያለበት ሁኔታ፣ተማሪዎችን ለመውጫ ፈተና ከማብቃት አኳያ የተሰጡ ሞዴል ፈተናዎች፣በተለያዩ ቴክኖሎጂዎች የመምህራንን አቅም ለማጎልበት የሚወርዱ የተለያዩ ሥልጠናዎች አፈፃፀምና በቀጣይ ወረቀት አልባ የመማር ማስተማር ሂደትን ለመከተል የእያንዳንዱ ኮሌጅ እያደረገ ያለው  ጥረት በተጨባጭ ቀርቦ ተገምግሟል። ጭብጥ ተኮር የምርምር ሥራዎች ከዕቅዱ አንፃር በሦስተኛው ሩብ ዓመት የተደረሰበትና በማህብረሰብ አገልግሎት በኩልም ኮሌጆች በተቀናጀ ሁኔታ የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት እያደረጉ ያሉበት ጥረትም ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል። በሪፖርት ግምገማው ወቅት በውስንነት ከተገመገሙት መካከል የትምህርት ፕሮግራሞች ኦዲትና ከእውቅና አሰጣጥ ጋር ተያይዞ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ኮሌጆች መሄድ ባለባቸው ልክ እየሄዱ ባለመሆኑ በተቋቋሙት ኮሚቴዎች አማካይነት በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገባ መመሪያ የተሰጠ ሲሆን ሪፖርትን በጊዜ አጠናቅሮ ከመላክ አንፃር የሚታዩ ክፍተቶች እንዲሻሻሉም የጽ/ቤቱ ኃላፊ ዶ/ር ተስፋዬ አሳስቧል።

events&news

Community Development Initiative Launched

BHU students and staff launched a community service program aimed at improving local health and education. The initiative will involve workshops, health screenings, and awareness campaigns across nearby villages. Date: March 25, 2026

events&news

BHU Signs MoU with ISAT U 🇪🇹🇵🇭

Bule Hora University has partnered with Iloilo Science and Technology University, Philippines, during the Global Partnership Conclave in India. The collaboration focuses on joint research, technology transfer, and faculty & student exchanges, strengthening global academic ties and cross-cultural innovation.

Scroll to Top