የተማሪዎች የጥሪ ማስታወቂያ ለውጥ

ጥቅምት 28/2016 ዓ.ም
በ2015 ዓ.ም በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በሪሜዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ስትከታተሉ ቆይታችሁ ማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች እና በ2014 ዓ.ም ትምህርት ጀምራችሁ በአንደኛ ሴሚስተር በውጤት እና በተለያዩ ምክኒያቶች ዊዝድረዋል (Withdrawal) በመሙላት ላቋረጣችሁ ተማሪዎች እንዲሁም በ2015 ዓ.ም በተሰጠው የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ት/ት ሚኒስቴር በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የመደባቸው ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ህዳር 1 እና 2/2016 ዓ.ም የተባለው ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ መሆኑንና በቅርቡ የምናሳውቃችሁ መሆኑን እንገልጻለን።
ቡሌ ሆራ ዩንቨርሲቲ

ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ

ጥቅምት 07/2016 ዓ.ም
ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ
ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ከዚህ በታች የተረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ  አመልካቾችን ባሉት ክፍት ስራ ቦታዎች /ለአካዳሚክ መምህርነት/ አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል። ስለሆነም
የሁሉም የስራ መደቦች የቅጥር ሁኔታ በውል ሆኖ በከፍተኛ ትምህርት ተቋም አስራር መሰረት ይሆናል
የደሞዝ ሁኔታ- በክፍተኛ ትምህርት ተቋማት የደሞዝ ስኬል መሰረት
ሴት ተወዳዳሪዎች ይበረታታሉ
ለወንድ MA/MSc (ሁለተኛ ዲግሪ) አመልካቾች CGPA 3.5 እና ከዚያ በላይ ሆኖ የመጀመሪያ ዲግሪ CGPA 3.0 እና ከዚያ በላይ ያለው
ለሴት  MA/MSc (ሁለተኛ ዲግሪ) አመልካቾች የMA/MSc CGPA 3.35 እና ከዚያ በላይ ሆኖ የመጀመሪያ ዲግሪ CGPA 2.75 እና ክዚያ በላይ ያላት

ለፕሬዝዳንትነት የወጣው ማስታውቂያ ውጤት

ነሃሴ 30/2015 ዓ.ም
ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት የስራ መደብ በወጣ ማስታወቂያ ያመለከታችሁ አመልካቶች የተጣራ የትምህርት ደረጃና የስራ ልምድ   ውጤታችሁ እንደምከተለዉ ተገልጿል ፡፡

Pages