የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ለወሎ ዩኒቨርሲቲ ድጋፍ አደርገ::

የወሎ ዩኒቨርሲቲ በጦርነቱ ምክንያት ዉድመት ከደረሰባቸው ዩኒቨርሲቲዎች መካከል አንዱ ነው። በትምህርት ሚኒስቴር እና ኒቨርሲቲዎች በጋራ ጥምረት የተቋማቱን ጉዳት በመለየትና መልሶ ለማቋቋም ዩኒቨርሲቲዎች በሶስት ክላስተር ስር ተዋቅረዋል፡፡ በዚሁ መሰረት የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ክላስተር ስር ካሉ ዩኒቨርሲቲዎች ዉስጥ አንዱ ሲሆን፤ለወሎ ዩኒቨርሲቲ መልሶ ማቋቋሚያነት ያግዛሉ የተባሉ ድጋፎችን አድርጓል፡፡ በመሆኑም ግምታዊ ዋጋቸው ከ1.5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የቁሳቁስ ድጋፍ ለወሎ ዩኒቨርሲቲ አስረክቧል።
በጅማ ዩኒቨርሲቲ መምህር እና የድጋፉ አስተባባሪ ኢንጅነር ጀማል ወርቁ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ጉዳት እኛንም ያሳስበናል በማለት በቻልነው አቅም ያለንን ለማካፈል መጥተናል ሲሉም ተናግረዋል ።

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ከምርምር ሥራ ጋር የተያያዘ ስልጠና

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ከምርምር ሥራ ጋር የተያያዘ ስልጠና
*******
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በፕሮፖዛል አዘገጃጀት፣ በፕሮጀክት አቀራረፅ እና ሌሎች ከምርምር ጋር ተያያዥነት ባላቸው ጉዳዮች ላይ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
ሥልጠናው የተሰጠው ከተለያዩ የዩኒቨርሲቲው ኮሌጆችና እንሰቲቲዩቶች ለተውጣጡ መምህራኖች ሲሆን፤ ሥልጠናው ከጥር 14-17/2014 ዓ.ም ላለፉት ሦሥት ቀናት በተከታታይ ሲሰጥ ቆይቶ ነጌ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ሥልጠናው የተዘጋጀው በምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕ/ጽ/ቤት ሲሆን፤ በዘርፉ ልምድና ዕውቀትን ያካበቱ ምሁራን ሥልጠናውን ለመምህራን ሲሰጡ ቆይተዋል።

College of Agricultural Sciences Experiences Sharing Program on topic “Publication Process and Procedures”

Bule Hora University, College of Agricultural Sciences has Organized Experiences Sharing Program on topic “Publication Process and Procedures” for his young staffs.
January 21/2022-BHU
Experiences sharing program was conducted by three senior staffs in the college (2 PhD and 1 Postdocs) and the participants were all academic staffs under the college.

የዋቢ መጽሐፍት ድጋፍ ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ትምህርት ቤት

የዋቢ መጽሐፍት ድጋፍ ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ትምህርት ቤት
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የህንድ አገር ተወላጅ መምህራን በአገራቸው OTF(Ontaro Teachers Federation) ከተባለ ድርጅት ጋር በመተባበር ሲሆን፤ ከ1ኛ-8ኛ እንዲሁም ከ9ኛ-10ኛ ክፍል የማጣቀሻ መጻሕፍት ድጋፍ ለትምህርት ቤቱ አስረክበዋል ። በድጋፍ የተበረከተው መጽሐፍት ብዛት ከ5-8ኛ ክፍል 480፣ ከ9-10ኛ ክፍል 280 በአጠቃላይ 760 መጽሐፍት ነዉ።

Pages