በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም የ4ኛ ሩብ ዓመትና የ12 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ እንዲሁም የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድን በተመለከተ ዉይይት ተካሄደ፡፡

ነሃሴ 01/2016 ዓ.ም

ዩኒቨርሲቲዉ በ2016 ዓ.ም ለማከናወን ያቀደዉን ዕቅድ ከመተግበር አንጻር በበጀት ዓመቱ አራተኛ ሩብ ዓመትን ጨምሮ የዓመቱ የሥራ ክንዉን በምን ደረጃ ላይ እንዳለ የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃኑ ለማን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮችና የየዘርፉ ኃላፊዎች በተገኙበት ተገምግሟል፡፡

ሪፖርቱ የቀረበዉ በዩኒቨርሲቲዉ የእስትራቴጂክ ጉዳዮች ሥራ አስፈፃሚ በአቶ መሰለ አለማየሁ ሲሆን በበጀት ዓመቱ በ4ኛ ሩብ ዓመት እና በ12 ወራት ዉስጥ የመማር ማስተማሩን ሥራ ጨምሮ ሌሎችንም ተግባራት በየግቡና በተቀመጠለት ስትራቴጅክ ዓላማ መሠረት በጠንካራ ጎን የተመዘገቡ እንዱሁም ዉስንነት የታዩባቸዉን ጉዳዮችና በትግበራ ወቅት ተግዳሮት የገጠማቸዉ እንደ ፋይናንሽያል ሪፖርት ጋር በማቀናጀት በዝርዝር አቀርበዉ ዉይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ/ም የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት የሚወስዱ የ”STEM”ተማሪዎችን መቀበል ጀመረ

ሀምሌ 27/2016 ዓ/ም

በዙሪያዉ ካሉት የተለያዩ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተወጣጡ እነዚህ ተማሪዎች ከየትምህርት ቤታቸዉ በትምህርት አቀባበላቸዉ ከሌሎች የተሻሉና እንዲሁም የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸዉ ወይም ልዩ ፍላጎት /Special Gift /talency/ ያላቸዉ መሆናቸዉን ቀደም ሲል ከነበረዉ የተማሪዎች ፕሮፋይል መረዳት ተችሏል።

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የክረምት በጎ አድራጎት ስራ በዩኒቨርሲቲዉ ተማሪዎች አስጀመረ።

ሀምሌ 27/2016 ዓ/ም

የሰላም ሚኒስቴር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በ2016 በጀት ዓመት የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እንዲሰጡ ቀደም ሲል በዩኒቨርሲቲዉ ደረጃ አሰልጥኗቸዉ የነበሩትን ተማሪዎች በማስተባበርና በመምራት የክረምት የበጎ አድራጎት ስራ /አገልግሎት/ እንዲሰጡ ከሀምሌ 27/2016 ጀምሮ የዩኒቨርሲቲዉን አጠቃላይ ቅጥር ግቢና የማስተማሪያ ሆስፒታል በማጸዳት አገልግሎቱን አስጀምረዋል።  የበጎ አድራጎት አገልግሎቱን ለማስኬድ በተቀመጠዉ አቅጣጫ መሰረት የዩኒቨርሲቲዉ ክፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የዘመቻዉ አላማና ግብ በበጎ አድራጎት ስራ ላይ ለተሳተፉ ተማሪዎች ስፋ ያለ ገለጻ የተሰጠ ሲሆን፣የበጎ አድራጎት ስራዉም በቀጣይነት በተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች መካከል በማዝመትና በመሰማራት እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል።

Pages