በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈፃሚ አስተባባሪነት በቡሌ ሆራ ከተማ ለበሪሶ ዱካሌ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሴት ተማሪዎች ሥልጠና ተሰጠ፡፡
Posted by admin on Friday, 17 January 2025ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 28/2017 ዓ.ም (BHU)
የዩኒቨርሲቲዉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚ በዩኒቨርሲቲዉ ያሉ ሴት ተማሪዎችን በተለያዩ መንገዶች ለማብቃት እየሠራ ካለዉ ሥራ በተጨማሪ በአካባቢዉ ያሉና በቀጣይ ወደ ዩኒቨርሲቲ
ይገባሉ ተብሎ የሚታመኑ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሴት ተማሪዎች ጭምር ከተለያዩ ፆታዊ ጥቃቶች እንዲሁም ከተላላፊ በሽታዎች ራሳቸዉን እንዲጠብቁ እገዛ ማድረጉ አስፈላጊ መሆኑ ታምኖ የተዘጋጀ ሥልጠና ስለመሆኑ በዕለቱ ተገልጾዋል፡፡