የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የመግቢያ ፈተና የሚወስዱትን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅቱን አጠናቋል።

መስከረም 24/2014 ዓ.ም
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የመግቢያ ፈተና የሚወስዱትን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅቱን አጠናቋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመግቢያ ፈተና በት/ቤቶች ሲሰጥ የቆየ ሲሆን ዘንድሮ የትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሰረት የ2014 የ12ኛ ክፍል በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሚማሩ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ፈተና ይወስዳሉ።

በቡሌ ሆራ  ዩኒቨርሲቲ የዩኒቨርሲቲው የአሥር ዓመት የሥራ  ዕቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ

25/12/2014
የቡሌ ሆራ  ዩኒቨርሲቲ  ፕሬዚዳንት ዶ/ር ታምሩ አኖሌ ከዩኒቨርሲቲው የካውንስል አባላት ጋር በዩኒቨርሲቲው የአሥር ዓመት የሥራ  ዕቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡ 
በውይይቱ የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዚዳንቶችን  ጨምሮ የካውንስል አባላቶች ተገኝተዋል፡፡ ከመማር ማስተማር፣ ከምርምር ፣ ከማህበረሰብ አገልግሎት ፣ ከኢንዱስትሪ ትሥሥር  እና ከአጠቃላይ ተቋማዊ የሥራ ትግበራ አንጻር ከ2010 እሰከ 2014 ዓ.ም ድረስ የዩኒቨርሲቲው የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በውይይቱ የቀረበ ሲሆን ከ2015 እሰከ 2024ዓ.ም የዩኒቨርሲቲውን የልህቀት ደረጃ ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀው የተቋሙ ዕቅድም ለካውንስል አበላቱ ቀርቧል፡፡ 

Pages