የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃኑ ለማ በ2017 ዓ.ም ሊተገበሩ የሚገቡ ቁልፍ ዉጤት አመላካች ሥራዎችና ተግባራት ዙሪያ ከየዘርፉ ም/ፕሬዝዳንቶች ጋር የሥራ ዉል ተፈራረሙ፡፡
Posted by admin on Friday, 17 January 2025ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 24/2017
በቅርቡ ትምህርት ሚኒስቴር ከአርባ ሰባት የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በ2017 የትምህርት ዘመን በሚተገበሩ ቁልፍ ዉጤት አመላካች ጉዳዮች ዙሪያ ከየፕሬዝዳንቶቻቸው ጋር የሥራ ዉል መፈራረሙ ይታወሳል፡፡
በዚሁ መሠረት የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃኑ ለማም በቀን 23/04/2017 ዓ.ም ከአካዳሚክ ምርምር; ቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህብረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት፤ከአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንትና እንዲሁም ከፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ ጋር የአፈፃፀም ዉል የፊርማ ሥነ ሥርዓት አከናዉኗል፡፡