የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃኑ ለማ በ2017 ዓ.ም ሊተገበሩ የሚገቡ ቁልፍ ዉጤት አመላካች ሥራዎችና ተግባራት ዙሪያ ከየዘርፉ ም/ፕሬዝዳንቶች ጋር የሥራ ዉል ተፈራረሙ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 24/2017
በቅርቡ ትምህርት ሚኒስቴር ከአርባ ሰባት የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በ2017 የትምህርት ዘመን በሚተገበሩ ቁልፍ ዉጤት አመላካች ጉዳዮች ዙሪያ ከየፕሬዝዳንቶቻቸው ጋር የሥራ ዉል መፈራረሙ ይታወሳል፡፡
በዚሁ መሠረት የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃኑ ለማም በቀን 23/04/2017 ዓ.ም ከአካዳሚክ ምርምር; ቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህብረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት፤ከአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንትና እንዲሁም ከፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ ጋር የአፈፃፀም ዉል የፊርማ ሥነ ሥርዓት አከናዉኗል፡፡

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም ክረምት ወቅት ላከናወነዉ በጎ አድራጎት ሥራዎች በሰላም ሚኒስቴር በኩል የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበርክቷል፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 23/2017

በሰላም ሚኒስቴርና በትምህርት ሚኒስቴር የበላይ አስተባባሪነት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ደረጃ በክረምቱ ወቅት የተለያዩ በጎ አድራጎት ሥራዎች እንዲሰሩ የተላለፈዉን ጥሪ ተከትሎ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የተቋሙን ማህብረሰብ በማሳተፍ ላከናወነዉ በጎ አድራጎት ሥራዎች እና ላስመዘገበዉ ዉጤት በሰላም ሚኒስቴር በኩል የምስጋና ምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡ 

Statistical Package for the Social Sciences (SPSS) and AMOS ›› በሚል ርዕስ ለመምህራን የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተሰጠ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም (BHU)
ሥልጠናዉ የተዘጋጀዉ በብዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ አስተባባሪነት ሲሆን ከተለያዩ የኮሌጁ ትምህርት ክፍሎች የተወጣጡ መምህራንና ሁለተኛ ድግሪያቸውን በተቋሙ እየተከታተሉ ያሉ ተማሪዎች ተሳታፊ ስለመሆናቸዉ ተገልጾዋል፡፡
በቦታው ላይ በመገኘት ስልጠናውን አስመልክተው መልዕክት ያስተላለፉት የብዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ዲን መ/ር ማንዶ ገናሌ ሲሆኑ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትኩረት ተሰጥቶኣቸው እየተከናወኑ ካሉት ተግባራት አንዱ በዋናነት የጥናትና ምርምር ሥራዎች መሆናቸውን በመጥቀስ እነዚህን የምርምር ሥራዎች በተሻሻሉ ሶፍትዌሮች በመደገፍ ጥራት ያላቸዉን የጥናትና ምርምር ሥራዎችን መምህራን እንዲሰሩ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ የአቅም ግንባታ ሥልጠና መሆኑን በንግግራቸው አመላክቷል፡፡

Research Methodology in Social Science: Quantitative and Qualitative research ``በሚል ርዕስ ስልጠና ተሰጠ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 19/2017 ዓ.ም (BHU)
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ደረጃ መምህራን ችግር ፈቺና ወቅታዊ የሆኑ የምርምር ሥራዎችን መሥራት ይችሉ ዘንድ ታሳብ ያደረገ በስነ-ሰብና ማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ አስተባባርነት በኮሌጁ ስር ካሉት የተለያዩ ኮሌጆች ለተመለመሉ መምህራን ለተከታታይ ሦስት ቀናት ተሰጥቷል፡፡

Pages