በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የግብርና እና እንስሳት ሕክምና ሳይንስ ኮሌጅ MSC (open Thesis Defense) እያደረጉ ይገኛሉ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 26/2017(BHU)
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የግብርና እና እንስሳት ሳይንስ ኮሌጅ የሁለተኛ ድግሪ ተመራቂ ተማሪዎች MSc in Agricultural economics, Msc in Soil Science, MSc in Sustainable Natural Resources Management ዙሪያ የመመረቂያ ጽሑፋቸዉን በዛሬዉ ዕለት ማቅረብ ጀምሯል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ የግብርና እና እንስሳት ሕክምና ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ዮሐንስ ኡርገሳ ፤ገምጋሚ መምህራንና ሌሎች ተጋባዥ መምህራን የተገኙ ሲሆን ዶ/ር ዮሐንስም በግብርናዉ ዘርፍ የተሻሻሉና በምርምር የተደገፉ የሥራዎችን በመሥራት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፏል፡፡

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት የ5ኛ ዓመት የክሊኒካል ፋርማሲ ተማሪዎች የተለያዩ በጎ አድራጎት ሥራዎችን አከናወኑ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 26/2017 ዓ.ም (BHU)
የኢንስቲትዩቱ 5ኛ ዓመት የክሊኒካል ፋርማሲ ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲዉ ቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህብረሰብ ጉድኝት ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር ላለፉት ሁለት ወራት ወደ ማህብረሰቡ በመዉረድ የተለያዩ በጎ አድራጎት ሥራዎችን በማከናወን አፈፃፀሙን በዛሬዉ ዕለት የኢንስቲትዩቱ አመራሮች፤መምህራንና ተማሪዎች በተገኙበት ገምግሟል፡፡

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ሳይንስ ኮሌጅ እየተሰጡ ባሉ የሁለተኛ ድግሪ ትምህርት ፕሮግራሞች ዙሪያ የሥርዓተ-ትምህርት ፍተሻ ዉይይት ተካሄደ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 21/2017 (BHU)
በመማር ማስተማሩ ሂደት የትምህርት ጥራቱንም ሆነ ተገቢነቱን ከማረጋገጥ አኳያ ከሚተገበሩ ተግባራት አንዱ በየደረጃዉ እየተሰጡ ባሉ የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ የሚደረግ የሥርዓተ-ትምህርት ፍተሻ አንዱ በወሳኝ ደረጃ ይታያል፡፡

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎችን ለመዉጫ ፈተና ከማዘጋጀት አኳያ ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ጋር የፓናል ዉይይት ተካሄደ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 21/2017 (BHU)
ትምህርት ሚኒስቴር በሀገር ደረጃ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በወሳኝ ደረጃ ካስቀመጣቸዉ የሪፎርም ሥራዎች መካከል ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሚመረቁ ተማሪዎች የሚሰጥ የመዉጫ ፈተና አንዱ ነዉ፡፡

Pages