በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ /College of Natural and Computational Science /አስተባባርነት በቅርቡ በሀገራችን እየተከሰተ ስለአለው የመሬት መንቀጥቀጥን አስመልክቶ ሴሚናር ተካሄደ፡፡

ጥር 07/2017 ዓ.ም

በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች የመሬት መንቀጥቀጥ እየተከሰተ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ለዩኒቨርሲቲውና ለአካባቢው ማህብረሰብ ግንዛቤ ለማስጨበጥ በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ”College of Natural and Computational Science ``አስተባባርነት የኮሌጁ መምህራን፤የትምህርት ክፍል ኃላፊዎችና ሠራተኞች በተገኙበት ሴሚናር ተካሂዷል፡፡

ማስታወቂያ

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ጥር 02/2017 ዓ.ም(BHU)
የመውጫ ፈተና ለምትጠባበቁ መምህራንና እጩ ተመራቂዎች በሙሉ::
በክረምት መርሓ ግብር በመምህርነት ሙያ ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ድግሪ የትምህርት እርከን ማሻሻያ ስልጠና ስትከታተሉ የቆያችሁና፤እንዲሁም በቅዳሜ እና እሁድ የትምህርት መርሓ ግብር ስትከታተሉ ቆይታችሁ የመውጫ ፈተናውን ያልወሰዳችሁ ሠልጣኞች፤የመውጫ ፈተና የሚሠጠው ከየካቲት 10-12/2017 ዓ.ም ስለሆነ ፈተናው የሚመለከታችሁ አካላት በሙሉ ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ አጥብቀን እናሳውቃለን፡፡
የአካዳሚክ ፕሮግራም ዳይሬክቶሬት

ኢንጅነሪንግ እና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ለላብራቶሪ ባለሙያዎች እና ለሁለተኛ ድግሪ ተማሪዎች በ‹‹ MATLAB››ሶፍት ዌር አጠቃቀም ዙሪያ ሥልጠና ተሰጠ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 28/2017 ዓ.ም (BHU)
የዩኒቨርሲቲዉ ኢንጅነሪንግ እና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ በስሩ ያሉትን የመምህራንና የባለሙያዎችን አቅም በተለያዩ አቅም ግንባታ ሥልጠናዎች ለማጎልበት የተለያዩ ስልቶችን ቀይሶ እየሰራ ይገኛል፡፡
በሥልጠናዉ ዕለት ተገኝቶ መልዕክት ያስተላለፉት የኢንጅነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ዲን መ/ር ቦሩ ቤደያ በኢንጅነሪንጉ ዘርፍ የሚከናወኑ ተግባራት ተያያዥነት ያላቸዉ በመሆኑ ለመምህራን እየተሰጠ ካለዉ የአቅም ግንባታ ሥልጠና በተጨማሪ ለላብራቶሪ ባለሙያዎች እና ለሁለተኛ ድግሪ ተማሪዎች መስጠቱ አስፈላጊ ሆኖ ስለታመነበት በ‹‹ MATLAB››ሶፍት ዌር አጠቃቀም ዙሪያ ሥልጠና መዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈፃሚ አስተባባሪነት በቡሌ ሆራ ከተማ ለበሪሶ ዱካሌ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሴት ተማሪዎች ሥልጠና ተሰጠ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 28/2017 ዓ.ም (BHU)
የዩኒቨርሲቲዉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚ በዩኒቨርሲቲዉ ያሉ ሴት ተማሪዎችን በተለያዩ መንገዶች ለማብቃት እየሠራ ካለዉ ሥራ በተጨማሪ በአካባቢዉ ያሉና በቀጣይ ወደ ዩኒቨርሲቲ
ይገባሉ ተብሎ የሚታመኑ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሴት ተማሪዎች ጭምር ከተለያዩ ፆታዊ ጥቃቶች እንዲሁም ከተላላፊ በሽታዎች ራሳቸዉን እንዲጠብቁ እገዛ ማድረጉ አስፈላጊ መሆኑ ታምኖ የተዘጋጀ ሥልጠና ስለመሆኑ በዕለቱ ተገልጾዋል፡፡

Pages