በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የመምህራን ማህበር ጠቅላላ ጉባዔ ተካሄደ፡፡
Posted by admin on Thursday, 9 October 2025መስከረም 22/2018 ዓ.ም :ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
በዩኒቨርሲቲዉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአዲስ መልክ የተመረጡት የመምህራን ማህበር ሥራ አስፈፃሚዎች ከተመረጡበት ጊዜ ወዲህ የተከናወኑትን ተግባራትና ሌሎችንም ጉዳዮች ጨምሮ የጉባዔዉ ተሣታፊ መምህራን በተገኙበት አቅርቦ ሰፊ ዉይይት ተካሂዷል፡፡
በማህበሩ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ፤ምርም፤ቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህብረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገበየሁ አሻግሬና የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አካሉ አሰፋ ተገኝቷል፡፡



















































