የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስቲር ዴኤታና የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ ሰቢሳቢ የሆኑት ዶ/ር ኬይረዲን ተዘራን ጨምሮ የቦርድ አባላት በዩኒቨርሲቲው እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችን አስመልክተው የመስክ ምልከታ አደረጉ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታኅሣሥ 5 ቀን 2017 ዓ.ም (BHU)
ቦርዱ ያደረገዉ የመስክ ምልከታ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲዉ ከሦስት ወራት በፊት ያለበትን የሥራ አፈፃፀም ደረጃ ከገመገመ በኃላ በቀጣይ ሦስት ወራት ዉስጥ መስተካከል አለባቸዉ ብሎ አቅጣጫ ባስቀመጠው መሠረት የተከናወኑ ሥራዎችን ታሳቢ ያደረገ የመስክ ምልከታ እንደሆነ በምልከታው ወቅት ተገልጾዋል፡፡

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ልዩ የስራ እቅድ ለ60 ቀናት በማዘጋጀት ሲያከናውን የቆየዉን የአፈጻጸም ሪፖርት ገመገመ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታኅሣሥ 3 ቀን 2017 ዓ.ም (BHU)
የአስ/ል/ም/ፕ በዘርፉ ከሚገኙ ዳይሬክቶሬቶች ስድስት ኮሚቴዎችን በማቋቋም በየዕለቱ የሥራ ክንውን እየገመገመ ክፍተት ባላቸዉ ላይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ሲያከናውን መቆየቱን ገልጿል፡፡

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የጽዳት ዘመቻ ተካሄደ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታህሣሥ 02/2017 (BHU)
በዩኒቨርሲቲዉ የተካሄደዉ የጽዳት ዘመቻ የተቋሙን ማህብረሰብ በአጠቃላይ ያካተተ ሲሆን ‹‹አከባቢያችንን ከቆሻሻ አዕምሮኣችንን ከጥላቻ እናጽዳ›› በሚል መሪ ቃል እንድካሄድ የተደረገ ሲሆን የዩኒቨርሲቲዉን ቅጥር ግቢ በስድስት ዋና ዋና ቦታዎች በመከፋፈል ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻዎችን የማስወገድ ተግባር ተከናዉኗል፡፡

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በ"College of Natural and Computational Science" የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ ተከሄደ ነው፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 01/2017(BHU)
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራትንና አግባብነትን ለማስጠበቅና ለማረጋገጥ እየተደረገ ባለው ጥረት ውስጥ የራሱን ድርሻ ለመወጣት የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ከሚሠጣቸው የትምህርት ክፍሎች መካከል በተወሰኑቱ ላይ የሥረዓተ ትምህርት ክለሳ እያደረገ ይገኛል። በያዝነው የትምህርት ዘመን በዩኒቨርሲቲው ባሉት የተለያዩ ኮሌጆች በሚሰጡ የትምህርት ፕሮግራሞች ዙሪያ የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ እየተደረገ ነው፡፡

Pages