በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ሕገ- ወጥ የሰዎች ዝውውርና የመንገድ ደህንነትን በሚመለከት ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ።
Posted by admin on Saturday, 19 July 2025ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፣ ግንቦት 26፣2017 ዓ.ም (ቡሆዩ)
የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናው በዩኒቨርሲቲው ማህብረሰብ አገልግሎት እንዲሁም በማህብረሰብ ሳይንስና ስነ ሰብ ኮሌጅ የጋራ ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን ከምዕራብ ጉጂ ዞን እና ከቡሌ ሆራ ከተማ አስተዳደር ፣የዞንና የከተማ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንቶች፣የዞንና የከተማ አቃበ ህግ ባለሙያዎች፣የዞንና የከተማ ትራንስፖርትና መንገድ ደህንነት ጽ/ቤት የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣የዞንና የከተማ ትምህርት ጽ/ቤቶች ባለሙያዎች፣ከሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት እና ከጉጂ ዞን የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳትፏል።



















































