በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ኮምፒዩቲንግና ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ አስተባባሪነት ``AI for Academic Research`` በሚል ርዕስ ዎርክ ሾፕ ተካሄደ።
Posted by admin on Saturday, 19 July 2025ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፣ ግንቦት 22፣2017 ዓ.ም (ቡሆዩ)
በዎርክ ሾፑ ላይ ኮምፒዩቲንግና ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ ከሁሉም ትምህርት ክፍሎች የተመለመሉ መምህራን የተሳተፉ ሲሆን ከተመራቂ የመጀመሪያ ዲግሪና ሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች መካከልም የተወጣጡ ተማሪዎች ስለ መሳተፋቸው ተገልፆዋል።
ዎርክሾፑን የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ያስጀመሩት የኮምፒዩቲንግና ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ ዲን መ/ር አሰፋ ሰንበቶ በአሁኑ ሰዓት እየኖርን ያለነው በዲጂታል ዓለም ውስጥ መሆኑንና ይህም ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ ለውጥ እያሳዬ መምጣቱን የጠቀሱ ሲሆን በሀገራት ኢኮኖሚ ዕድገት ዙሪያም ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ስለመሆኑ አስረድቷል።


















































