በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ለ2015 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና በአስፈታኝነት ለተመደቡ አካላት ገለፃ (Orientation) ተሰጠ፡፡

የ2015 ዓ.ም የሀገር አቀፍ ፈተናን በሚመለከት ከትምህርት ሚኒስቴርና ከሀገር አቀፍ ፈተና ኤጄንሲ ፈተናውን ከማስፈፀም አኳያ የተሰጠውን መግለጫ በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ከአስተባባሪዎች ጀምሮ እስከ ፈታኝ ድረስ ያሉት በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ ኦዳ አዳራሽ በመገኘት መግለጫውን ተከታትለዋል፡፡
ከትምህርት ሚኒስቴርና ከፈተና ኤጄንሲ በቀጥታ በቪዲዮ(virtual) ከተላለፈው መግለጫ በተጨማሪ ከማዕከል በመጡ አስተባባሪዎችና በዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃኑ ለማ አማካኝነት ገለፃው የተሰጠ ሲሆን በገለፃው ላይም 77 ሴንተር ቺፍ፣ 87 ሱፐርቫይዘሮች፣ 484 ፈታኞችና ሌሎችም ከፈተናው ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸዉ አካላት መሳተፋቸውን ከአካዳሚክ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ሙያዎች ሲያሰለጥናቸዉ የቆየዉን ተማሪዎች ለ10ኛ ዙር አስመርቋል፡፡

ሐምሌ 13/2015 ዓ.ም 
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ሙያዎች ሲያሰለጥናቸዉ የቆየዉን ተማሪዎች ለ10ኛ ዙር አስመርቋል፡፡

Pages