ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ መጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች የሕይወት ክህሎት ሥልጠና ተሰጠ፡፡
Posted by admin on Friday, 17 January 2025ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 08/2017
ሥልጠናዉ የተዘጋጀው በዩኒቨርሲቲዉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈፃሚ አስተባባርነት ሲሆን ሥልጠናው በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በዩኒቨርሲቲዉ ካሉት የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች በተወጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎች ተሰጥቷል፡፡
በሥልጠናዉ ላይ ተገኝተዉ ተገቢውን መልዕክት ያስተላለፉት የዩኒቨርሲቲዉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሪት ተስፋነሽ ኢዴኤ ሲሆኑ የሥልጠናዉ ዓለማ ወደ ዩኒቨርሲቲዉ እየገቡ ያሉ ተማሪዎች በዕዉቀትና በክህሎት ላይ የተመሠረቱ ዉሳኔዎችን የመወሰን ብቃት በማዳበር በህይወታቸዉ ዉስጥ የሚገጥማቸዉን ፈተናዎች ወደ መልካም አጋጣሚዎች በመቀየር ለዉጤት እንዲበቁ ታስቦ የተዘጋጀ ሥልጠና ስለመሆኑ አስረድቷል፡፡