በዩኒቨርሲቲዉ የአካዳሚክ ምርምር የቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት እና በኢንጂነሪንግ ኮሌጅ ዲን የተመራውና እንድሁም በኮልጁ ስር ከሚገኙ ከተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ጋር በመሆን ጉብኝት ተካሄደ።
Posted by admin on Friday, 17 January 2025ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ ታህሳስ 12/2017 ዓ.ም (BHU)
በጉብኝቱም ወቅት የዩኒቨርሲቲዉ አካዳሚክ ምርምር የቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገበየሁ አሻግሬ እና የኢንጂነሪንግ ኮሌጅ ዲን መ/ር ቦሩ በዴያ እንዲሁም የኮሌጁ የተለያዩ የትምህርት ክፍሎች መምህራን በተገኙበት የተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ተጎብኝተዋል።
የጉብኝቱም አላማ በኮሌጁ የሚገኙ የትምህርት ክፍሎች አሁናዊ ሁኔታዎችን መፈተሽን ዓላማ ያደረገ ጠንካራና ደካማ ጎኖች ተለይተው ጠንካራውን በምን መልኩ ማሰቀጠል እንዳለባቸውና እንድሁም እንደ ክፍተት የታዩትን ደካማ ጎኖች ደግሞ እንዴት ማሻሻል አንደሚቻል አቅጣጫ ያስቀመጡበት ሁኔታ የተፈጠረ ሲሆን፣በተጨማሪም በዘለቄታነት የኮሌጁን ችግሮች መፍታትና የትምህርት ጥራት ላይ በማተኮር ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋ በማፍራት ዓላማው እንዲቀጥል አቅጣጫ ተቀምጦ ጉብኝቱን አጠናቋል ።