የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም ክረምት ወቅት ላከናወነዉ በጎ አድራጎት ሥራዎች በሰላም ሚኒስቴር በኩል የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበርክቷል፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 23/2017

በሰላም ሚኒስቴርና በትምህርት ሚኒስቴር የበላይ አስተባባሪነት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ደረጃ በክረምቱ ወቅት የተለያዩ በጎ አድራጎት ሥራዎች እንዲሰሩ የተላለፈዉን ጥሪ ተከትሎ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የተቋሙን ማህብረሰብ በማሳተፍ ላከናወነዉ በጎ አድራጎት ሥራዎች እና ላስመዘገበዉ ዉጤት በሰላም ሚኒስቴር በኩል የምስጋና ምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡