በቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ የማተማሪያ ሆስፒታል ለአምስት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየው የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ጥገና አገልግሎት ተጠናቀቀ ።

ሀምሌ 17/2016 ዓ/ም

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ የማስተማሪያ ሆስፒታል ከሂማሊያን ካታራክት ፕሮጀክት (HCP) ጋር በመሆን ለአምስት ተከታታይ ቀናት የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ጥገና ሲሰጥ ቆይቷል።በስራው ሂደት ካጋጠሙ የተለያዩ ክስተቶች መካከል አንዱ ከአንድ ቤተሰብ አምስት የዓይን ሞራ ግርዶሽ ህሙማን የተገኙ ሲሆን፣ ለሁለቱ የህክምና እርዳታ ተደርጎላቸዉ ማዬት የቻሉ ሲሆን ሶስቱ ህሙማን ግን ለተጨማሪ የህክምና እርዳታ ወደ ምኒልክ ሆስፒታል የተላኩ መሆናቸው ተገልጿል።  በተመሳሳይ መልኩ ሁለቱም ዓይኖቻቸዉ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ያለባቸው 115(አንድ መቶ አስራ አምስት) ህሙማን የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ጥገና የተደረገላቸዉ ሲሆን፣በዚህ ዙር በአጠቃላይ በአምስቱ ቀናት ዉስጥ 621 (ስድስት መቶ ሃያ አንድ) ህሙማን የህክምና አገልግሎት ማግኘታቸዉ ተገልጿል።

የGAT(Graduate Admission Test) ስልጠና ለመውሰድ ለተመዘገባችሁ በሙሉ፣

ቀን 15/2016 ዓም
ማስታወቂያ

ስልጠናው የሚሰጠዉ ሀምሌ 19 እና 20/2016 ዓ/ም ለተከታታይ ሁለት ቀናት ስለሆነ ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ በመያዝ በተጠቀሰዉ ቀን በግቢዉ በሚገኘዉ አባጡንጋ መታሰቢያ አዳራሽ በአካል ተገኝታችሁ ስልጠናውን እንድትከታተሉ እናሳዉቃለን።

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ የማስተማሪያ ሆስፒታል የዓይን ህሙማንን የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ጥገና አገልግሎት መሰጠት ተጀመረ።

ሀምሌ 08/2016 ዓ/ም

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ የማስተማሪያ ሆስፒታል፣የጤና ሳይንስ እንስቲትዩትና የህማሊያን ካታራክት ፕሮጀክት (HCP) (መንግታዊ ያልሆነ ድርጅት) ጋር ተባብሮ መስራት ከጀመረበት ከ2015 ዓ/ም ጀምሮ እስካሁን ከአንድ ሺህ ሁለት መቶ በላይ የዓይን ህሙማንን የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ጥገና ያደረገ ሲሆን፣ ከዛሬ ሐምሌ 8-12/2016 ድረስ ለአምስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የህክምና አገልግሎት ከአራት ዞኖች ለሚመጡ ከ600 በላይ ህሙማን የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ጥገና ለመስጠት ስራ መጀመራቸውን የቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ እንስቲትዩት ቺፍ ኤክስኩዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ሳፋይ ኤለማ አስታውቀዋል ።

Pages