Statistical Package for the Social Sciences (SPSS) and AMOS ›› በሚል ርዕስ ለመምህራን የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተሰጠ፡፡
Posted by admin on Friday, 17 January 2025ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም (BHU)
ሥልጠናዉ የተዘጋጀዉ በብዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ አስተባባሪነት ሲሆን ከተለያዩ የኮሌጁ ትምህርት ክፍሎች የተወጣጡ መምህራንና ሁለተኛ ድግሪያቸውን በተቋሙ እየተከታተሉ ያሉ ተማሪዎች ተሳታፊ ስለመሆናቸዉ ተገልጾዋል፡፡
በቦታው ላይ በመገኘት ስልጠናውን አስመልክተው መልዕክት ያስተላለፉት የብዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ዲን መ/ር ማንዶ ገናሌ ሲሆኑ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትኩረት ተሰጥቶኣቸው እየተከናወኑ ካሉት ተግባራት አንዱ በዋናነት የጥናትና ምርምር ሥራዎች መሆናቸውን በመጥቀስ እነዚህን የምርምር ሥራዎች በተሻሻሉ ሶፍትዌሮች በመደገፍ ጥራት ያላቸዉን የጥናትና ምርምር ሥራዎችን መምህራን እንዲሰሩ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ የአቅም ግንባታ ሥልጠና መሆኑን በንግግራቸው አመላክቷል፡፡