ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲቲና የኢትዮጵያ ደን እና ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 07/2018 ዓ.ም ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ

ዩኒቨርሲቲው በአካባቢው ያለውን ብዝሃ ሕይወት በአግባቡ በመጠበቅ ከቱርዝም የሚገኘው ገቢ የሀገር ኢኮኖሚን መደገፍ እንዲችል ከደን እና ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ከባልሥጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ኩመራ ዋቅጀራ ጋር የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ፣ምርምር፣ቴክኖሎጅ ሽግግርና ማህብረሰብ አግልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገበየሁ አሻግሬ ተፈራርሟል።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ከፋነ - አጋ ፋዉንዴሽን ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ፡፡

ህዳር 20/2018 ዓ.ም፡ ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ

ይህ ምሥረታ ወይም ፋዉንዴሽኑ ህዳር 23/2016 ዓ/ም በይፋ ስራ የጀመረ ሲሆን ፤ የተቋቋመበት ዋና ዓላማ ቀደም ሲል 72ኛ የጉጂ አባ ጋዳ በነበሩና የክብር ዶኮቶሬት ተሸላሚ በዩባ አጋ ጤንጤኖ ተጀምሮ የነበረዉን ሪዕይ በማስቀጠል፣ ነባሩን የገዳ ስርዓት ባህላዊ እሴቶቹን ሳይለቅ እንዲጠናከር መስራት፤ የባህል ማዕከላትን ማደራጀት የመሳሰሉ ተግባራትን ማከናወን ሲሆን የታለመለትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ ደግሞ ከቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የገዳ እና ባህል ጥናት እንስቲትዩት ጋር በአጋርነትና በትብብር በገዳ ስርዓት ዙሪያ አብሮ ለመስራት ይህ የመግባቢያ ሠነድ በዩኒቨርሲቲ ደረጃ ተፈርሟል።

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኮሌጅ የጤና ባለሙያዎች 27ኛዉን የጤና ዘርፍ ዓመታዊ ጉባኤ በበየነ መረብ ተከታተሉ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ፣ ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም (ቡሆዩ)

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት አመራሮችና ባለሙያዎች በጅማ ከተማ ''ዘላቂ ኢንቨስትመንት እና ኢኖቬሽን ለጠንካራ ጤና ሥርዓት '' በሚል መሪ ቃል የተካሄደውን 27ኛውን የጤና ዘርፍ ዓመታዊ ጉባዔ በበይነ መረብ በቀጥታ ተከታትሏል።

በከተማዋ የተካሄደዉ ይህ ዓመታዊ ጉባኤ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሆን የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት አመራሮችና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትም ባሉበት ሆነዉ ከጥቅምት 13-14/2018 ለሁለት ቀናት በበይነ መረብ ተከታትሏል ።

Pages